Friday, 4 September 2015

ማንኛውም ክርስቲያን ነኝ የሚል አማኝ ሊክዳቸው የማይገቡ ሦስት እውነታዎች

ማንኛውም ክርስቲያን ነኝ የሚል አማኝ ሊክዳቸው የማይገቡ ሦስት እውነታዎች

1. አንድ ብቸኛ እግዚአብሔር አለ

ኢሳ.45፥5 እኔ እግዚአብሔር ነኝ ከእኔም ሌላ ማንም የለም ከእኔም በቀር አምላክ የለም
በፀሐይ መውጫና በምዕራብ ያሉ ከእኔ በቀር ማንም ሌላ እንደሌለ ያውቁ ዘንድ አስታጠቅሁህ፥
አንተ ግን አላወቅኸኝም እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ ከእኔም ሌላ ማንም የለም።
ሚል.2፥10 ለሁላችን አንድ አባት ያለን አይደለምን? አንድ አምላክስ የፈጠረን አይደለምን?
ኤፌ.4፥6 ከሁሉ በላይ የሚሆን በሁሉም የሚሠራ በሁሉም የሚኖር አንድ አምላክ የሁሉም
አባት አለ።

2. አንዱ እና ብቸኛው እግዚአብሔር በስጋ ተገለጠ

1ጢሞ.3፥16 እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ የተገለጠ፥
በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥ በክብር ያረገ።
ዮሐ.1፥1 በመጀመሪያው ቃል ነበረ፥ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፥ ቃልም እግዚአብሔር
ነበረ።
ዮሐ.1፥14 ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ፥ አንድ ልጅም ከአባቱ
ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን።

3. ኢየሱስ አንዱ እና ብቸኛው እግዚአብሔር ነው

ማቴ.1፥23 እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታልየተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚልነው።ዮሐ.10፥31 አይሁድ ሊወግሩት ደግመው ድንጋይ አነሡ።ኢየሱስ፦ ከአባቴ ብዙ መልካም ሥራአሳየኋችሁ፤ ከእነርሱ ስለ ማናቸው ሥራ ትወግሩኛላችሁ? ብሎ መለሰላቸው። አይሁድም። ስለመልካም ሥራ አንወግርህም፤ ስለ ስድብ፤ አንተም ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለ ማድረግህነው እንጂ ብለው መለሱለት።ዮሐ.20፥28 ቶማስም። ጌታዬ አምላኬም ብሎ መለሰለት።
(And Thomas answered and said unto him, My Lord and my God.)


Wednesday, 18 February 2015

የኖህ መርከብ


በመጽሐፍ ያሉትን ፤ህግጋትን ሁሉ
አንዳች ሳታጓድል ሁሉ እንዲያሁ እንዳሉ
የምትጠብቅ ብትሆን አምላክን ‘ምትፈራ
ለምስኪኖች አዛኝ ልብህ የሚራራ
አምላክን አምላኪ ምጽዋአድራጊ
ጸላይ ጸሎተኛ ሌት ተቀን ማይተኛ
ብትሆን እንዲ ዓይነት ሰው
ስለ ጽድቅ የገባው
ይህ ሁሉ ልፋትህ መስዋዕነትህ
ፍሬ እንዲያፈራ አክሊል እንዲኖርህ
ከሚመጣው ቁጣ ነፍስህለማዳን
ከቅዱሳን ጋራ ባለሀገር መባል
መታሰቢያ ሳይሆን እንዲሆን ለመዳንህ
ነውርና ነቀፋ ተንኮል የሌለባት
በመንፈስ ቀድሶ በደሙ የዋጃት፤
እንዳትነቃነቅ በዓለት ላይ ያጸናት
አምላኳን ‘ምትመስል ለእርሱ የተዘጋጀች
የዚህን ዓለም ውጊያ በድል ያሸነፈች
አንድ ታናሽ መንጋ እርስት የተሰጣት፤
በእርሷ ውስጥ ለሚኖር ሰላም እረፍት ያላት
የቀደመች መንገድ የሐዋርያት የነቢያት
ይህች መሰረት መፈለግ መመርመር መያዝም አለባት።
ለሰው ልጆች መዳን በአምላክ የተሰራች
በዚህች ምድር ላይ ቤተክርስቲያናችን የኖህ መርከብ አለች።

Tuesday, 13 January 2015

ያብብ ምድረበዳው

   በወ/ም አክሊሉ                        

                      ያብብ ምድረ በዳው

እሾኽ አሜኬላ ኩርንችት ሞልቶበት
ጣዖት አድመኝነት ጊንጥ እባብ በዝቶበት
ድርቅና ውሃ ጥም እጅግ የከፋበት
ብርሃን ደብዛው ጠፍቶ ቀኑ የጨለመበት
ይታሰብ ምድረ በዳው ጸሎታችን ያርግ
እንጭሁ ወደ ጌታ እጃችን ይዘርጋ
                       ይመስረት አለቱ ይነገር እውነቱ
                       ይታይ ጭላንጭሉ ይብራ ወጋገኑ
                       ወንጌል ካልተዘራ አጭር ነው ዘመኑ።
መሬቱ ይረስርስ ደመናውም ይታይ
ምድረበዳው ያብብ ሁሉም ወንጌል ያንግብ።

Monday, 12 January 2015

እግዚአብሔር የሚወዳቸው እና እግዚአብሔር የሚጠላቸው ነገሮች ከመጽሐፍ ቅዱስ

  በወ/ም አክሊሉ
እግዚአብሔር የሚወዳቸው ነገሮች
                         ከመስዋዕት ይልቅ ምህረትን     ሆሴ.6፥6  
ምህከል                 ከልብ ይቅር ማለትን            ማቴ.6፥14
             ንሰሐ መግባትን                 ራእ.3፥3
             በብርሃን መመላለስን           ኤፌ.5፥6
             ርኁሩህ መሆንን                ኤፌ.4፥12
             ራስን ማዋረድን                 1ነገ.20
             ወንድምን መውደድን           1ዩሐ.3፥14
             ደግ መሆንን                    ማቴ.12፥35
             ስጦታ መስጠትን               ሉቃ.6፥38
             ገርነት                           ፊልጲ.4፥5
             ጠንካራ ክርስቲያን መሆንን    ዘዳ.13፥30
            ለበላይ መታዘዝን               ዕብ.13፥17
            አንድ ልብ መሆንን             ሐዋ.4፥32
            መተሳሰርን                      ኤፌ.4፥3
            እርስ በርስ መዋደድን          ሮሜ 13፥8
            ጠንቃቃ መሆንን               ዕብ.4፥12
            ወደ ፊት መጓዝን               1ጢሞ.4፣15
            ማመስገንን                      ኤፌ.5፥20
            እውነት መናገርን                 ኤፌ.4፥25
            በቅድስና መኖርን                1ጴጥ.1፥16
            ራስን ሆኖ መገኘትን             ኢዩ.37፥7
            መልካም ወሬ ማውራትን       ምሳ.13፥30
            ከእርሱ ጋራ መሆንን            2ዜና.15፥2
            መዘመር፣መጸለይና መጾምን    መዝ.105፥1
            መቀደስን                        ራእ.22፥14
            አሸናፊነትን                      ዘኁ.13፥30
            መፈተንን                        ያዕ.1፥12
            እርሱን ተስፋ ማድረግን        መዝ.36፥7
            አስተዋይነትን                   ሆሴ.4፥14
            ማገልገልን                      ኢዮ.36፥11
            እርሱ የቀባቸውን ማክበርን    ሮሜ 12፥10
            እሺ ማለትን                    ኢሳ.1፥18
            ሃይማኖትን መጠበቅን         2ጢሞ.4፥7
            በስርዓት መሄድን              2ተሰ.3፥6
            ወንጌል መመስከርን            ሮሜ10፥10
       እግዚአብሔር የሚጠላቸው ነገሮች 
ምህረ       ምህረት አለማድረግን            ማቴ.18፥32
ቂም መያዝን                    ማቴ.18፥35
 አመጸኝነትን                    2ተሰ.3፥10
በጨለማ መመላለስን          1ዩሐ.3፥11
መበቀልን                      ሮሜ 12፥19
ራስን ከፍ ማድረግን           ሉቃ.14፥11
ወንድምን መጥላትን           1ዩሐ.3፥15
ክፉ መሆንን                   ማቴ.12፥35
ንፉግነትን                      ምሳ.11፥24
እልከኝነት                      ዕብ.3፥13
ደካማ ክርስቲያን መሆንን      ዘኍ.13፥33
ለበላይ አለመታዘዝን           ዘኍ.16፥2
መለያየትን                      ምሳ.18፥1
መበታተንን                     ገላ.5፥15
እርስ በርስ መጠላላትን        ገላ.5፥15
ግድ የለሽነትን                  1ሳሙ.3፥13
ወደኋላ መጓዝን                ዘፍ.19፥17
ማጉረምረምን                   ዘፍ.14፥27
ውሸት መናገርን                ዩሐ.8፥44
ኃጢያት መስራትን             ሕዝ.18፥17
ግብዝነትን                     ማቴ.23፥23
ክፉ ወሬ ማውራትን          2ሳሙ.13፥3-5   
እርሱን መተውን              2ዜና 15፥3
አለመዘመር፣አለመጸለይና አለመጾምን
መርከስን                       ራእ.22፥11
ተሸናፊነትን                    2ጴጥ.2፥19
በፈተና ወድቆ መቅረትን       ዘዳ.2፥8
ተስፋ መቁረጥን                1ተሰ.4፥13
ዝንጉነትን                       ኢዮ.13፥16
አለማገልገልን                  
እርሱ የቀባቸውን መዳሰስን    መዝ.104፥14
እምቢ ብሎ ማመጽን           ኢሳ.1፥18
ሃይማኖት መካድን              1ሳሙ.3፥13
በስርዓት አለመሄድን            2ተሰ.5፥1
የእርሱን በጎነት አለመናገርን     1ጴጥ.2፥9
         አምላካችሁም እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ፥ ቍጣው የዘገየ፥ ምሕረቱም የበዛ፥ ለክፋትም የተጸጸተ ነውና ወደ እርሱ ተመለሱ።                        ኢዩ.2፥13
                          ጌታ ኢየሱስ በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይስጠን። አሜን





,            














Wednesday, 6 August 2014

የክርስቶስ ትምህርት




በኢዮስያስ ሽመልስ
 ለሚወጣ ሁሉ በክርስቶስም ትምህርት ለማይኖር ሰው አምላክ   የለውም፤ በክርስቶስ ትምህርት ለሚኖር አብና ወልድ አሉት።
                                                     1ዩሐ.1፥9
ምድር ላይ ኃያሌ በክርስትና ስም የሚንቀሳቀሱ የእምነት ተቋማት እንዳሉ ይታወቃል። ነገር ግን የቱንም ያህል በቁጥር ይበርክቱ እንጂ አንድ እውነተኛ መንገድ እንዳለች መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳናል።
በመጠራታችሁ በአንድ ተስፋ እንደ ተጠራችሁ አንድ አካልና አንድ መንፈስ አለ፤ አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት፤ከሁሉ በላይ የሚሆን በሁሉም የሚሠራ በሁሉም የሚኖር አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለ። (ኤፌ.4፥4)
በመሆኑም እውነቱን ከውሸቱ ለመለየት እንዲቻለን የክርስትና ትምህርት የትኛው ነው? ለሚለው ጥያቄ ትክክለኛ መልስ ማግኘት ይኖርብናል። ይህን ማድረግ ከተቻለን እውነት ወደምትመስል ሳይሆን ወደ እውነተኛይቱ መንገድ መመለስ እንችላለን።
          ለሰው ቅን የምትመስል መንገድ አለች ፍጻሜዋ ግን የሞት መንገድ ነው።(ምሳ.14፥12) ከዚህ እንደምንረዳው በሰው አስተሳሰብ እውነት የሚመስሉ ሁሉ መጨረሻቸው ሞት እንደሆነ ነው።

        የክርስትና ትምህርት የትኛው ነው?

  ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ላይ በኖረበት ሰላሳ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር እውነተኛውን የክርስትና ትምህርት ለደቀመዛሙርቱ አስተምሯል። እንዲሁም በምኵራብ እና ህዝብ በተሰበሰበባቸው ቦታዎች ማስተማሩን መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል።
ወደ ቅፍርናሆምም ገቡ፤ ወዲያውም በሰንበት ወደ ምኵራብ ገብቶ አስተማረ።(ማር.1፥21)
በመቀጠልም ለሰው ልጆች ነፍስ ሊከፍል ያለውን ዋጋ ከጨረሰ በኃላ የመዳንን ወንጌል ለሐዋርያት ሰጥቷል።ከዚህም በኋላ ኢየሱስ ራሱ ለዘላለም ድኅነት የሆነውን የማይለወጠውን ቅዱስ ወንጌል ከፀሐይ መውጫ እስከ መጥለቂያው ድረስ በእጃቸው ላከው።(ማር.16፥8)
ወንጌልን እንዲያስተምሩ ስልጣን ከተሰጣቸው  ሐዋርያት መካከል የመንግስተ ሰማይ ቁልፍ የተሰጠው ጴጥሮስ መዳን የሚገኝበትን መንገድ ሲያስተምር፦
ጴጥሮስም፦ ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ።(ሐዋ.ሥራ 2፥38)
ቁ.41 ቃሉንም የተቀበሉ ተጠመቁ፥ በዚያም ቀን ሦስት ሺህ የሚያህል ነፍስ ተጨመሩ፤
ከላይ መረዳት እንደምንችለው በአንድ ቀን ሦስት ሺህ  ነፍስ ከኃጢያት እና ከሞት እስራት ሊፈቱ የቻሉበት ቁልፍ ንስሐ፥የኢየሱስ ክርስቶስ ስም ጥምቀት እና  የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ነው። ይህንን  መጽሐፍ ቅዱሳዊ የመዳን አስተምህሮ የማይቀበል ማንኛውም ስመ ክርስቲያን መሳሳቱን አምኖ መመለስ ይኖርበታል። በተጨማሪ በሐዋ.ሥራ 11፥26 ክርስቲያን የሚለውን ስያሜ ያገኙት በቤተክርስቲያን ሲያስተምሩ የቆዩት ደቀመዝሙርት ነበሩ።
በቤተ ክርስቲያንም አንድ ዓመት ሙሉ ተሰበሰቡ፥ ብዙ ሕዝብንም አስተማሩ፤ ደቀ መዛሙርትም መጀመሪያ በአንጾኪያ ክርስቲያን ተባሉ።(በሐዋ.ሥራ 11፥26)
ስለዚህ ማንም ሃይማኖተኛ እራሱን እና ተከታዮቹን ክርስቲያኖች ብሎ ቢጠራም የሐዋርያት ትምህርትን ከጣለ ኢየሱስን የጣለ በመሆኑ ምክኒያት አብ አይኖረውም ክርስቲያንም ሊባል አይችልም።
የሚሰማችሁ እኔን ይሰማል፥ እናንተንም የጣለ እኔን ይጥላል፤ እኔንም የጣለ የላከኝን ይጥላል።(ሉቃ.10፥16)
የእግዚአብሔርን መንግስት ከሚያስወርሰው ትክክለኛ መንገድ ውጪ  ሌላ አቋራጭ መንገድ የለም። መሰረቱም አንድ መሰረት የሐዋሪያት እና የነቢያት መሰረት ነው።
በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል፥ የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።(ኤፌ.2፥20)
አንዴ ከተመሰረተው መሰረት ውጪ መመስረት ዋጋው በእሳት መቃጠል መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል።
ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልምና፥ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።(1ቆሮ.3፥11)
በተለያዩ ዘመናት በሚነሱ ሐሰተኛ ነቢያት የፍልስፍና አስተምህሮ እንዳንስት ሐዋርያው ጳውሎስ ሲመክረን፦
እንደ ክርስቶስ ትምህርት ሳይሆን፥ እንደ ሰው ወግና እንደ ዓለማዊ እንደ መጀመሪያ ትምህርት ባለ በፍልስፍና በከንቱም መታለል ማንም እንዳይማርካችሁ ተጠበቁ።(ቆላ.2፥8) ይለናል።
ከሐዋርያት ትምህርት ውጪ ሌላው ልዮ ወንጌል እና የተረገመ  በመሆኑ ተከታዮቹን ሊያፀድቅ ከቶ አይቻለውም!!
እርሱ ግን ሌላ ወንጌል አይደለም፤ የሚያናውጡአችሁ የክርስቶስንም ወንጌል ሊያጣምሙ የሚወዱ አንዳንዶች አሉ እንጂ።ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን።(ገላ.1፥8)


ማጠቃለያ
ሰዎች ሁሉ ይድኑ ዘንድ የእግዚአብሔር ፍቃድ ነው።(1ጢሞ.2፥3-4) ስለዚህም ሰው ሁሉ ወደ እውነት እንዲመጣ ኢየሱስ ይታገሳል።
ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል።(2ጴጥ.3፥9)
     እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ እነርሱ ግን፦ አንሄድባትም አሉ።እኔም የመለከቱን ድምፅ አድምጡ ብዬ ጠባቆችን ሾምሁባችሁ እነርሱ ግን፦ አናደምጥም አሉ።(ኤር.6፥16)
ዛሬ ይህንን ጽሑፍ የምናነብ ሁሉ ለእግዚአብሔር ቃል ታዛዠ በመሆን ለነፍሳችን የዘላዓለም እረፍትን ለማግኘት እንድንችል ጌታ ኢየሱስ ይርዳን። አሜን!!!